ምዝገባ

እባክዎን በ UNHCR የሚሰጡ ሁሉም አገልግሎቶች፣ ምዝገባን ጨምሮ፣ በነጻ እንደሚሰጡ ይወቁ።

በሊቢያ ውስጥ የመጠለያ ፈላጊዎች ምዝገባ በUNHCR ይካሄዳል። የሊቢያ ባለስልጣኖች ለUNHCR ከተወሰኑ ዜጎች ብቻ ሰዎችን እንዲመዝግብ ፍቃድ ይሰጣሉ።

በ0911633466 ያለውን የምዝገባ ስልክ መስመር መደወል ወይም በWhatsApp 0910019417 / 0916998581 መገናኘት ይችላሉ፤ የምዝገባ ሰራተኞችም ስለ ምዝገባ ሂደቶች መመሪያ ይሰጣሉ። ተገቢ ከሆኑ፣ ከUNHCR ሰራተኞች ጋር በትሪፖሊ ወይም በሌላ የምዝገባ ቦታ ለመገናኘት ቀጠሮ ይሰጥዎታል። በምዝገባ ቃለ-መጠይቁ ወቅት፣ UNHCR ስለ እርስዎ መረጃ ይሰበስባል፣ ይህም ስምዎን፣ የትውልድ ቀንዎን፣ የትውልድ ቦታዎን እና ከአገርዎ ለመውጣት ያስነሳዎትን ምክንያት ያካትታል።

 

በምዝገባ ቀን ሁሉም የቤተሰብዎ አባላት (ባል/ሚስት፣ ልጆች ወይም ሌሎች ቅርብ ዘመዶች) ከእርስዎ ጋር መሆን አለባቸው።

ካሉዎት ሁሉንም ዋና (original) ሰነዶች ማምጣት አለብዎት፣ እነዚህም ይካተታሉ:

  • ፓስፖርት

  • የመንግስት መታወቂያ ካርድ

  • የልደት ማስረጃ

  • የሥራ ፍቃድ

  • ከጋብቻ ሁኔታ ጋር የተያያዙ ሰነዶች

  • የትምህርት መዝገቦች

  • ከUNHCR ወይም ከሌሎች መንግስታት የተሰጡ የስደተኛ ወይም የመጠለያ ፈላጊ ማስረጃዎች

  • ስለ መለያዎ ሌሎች የመንግስት ሰነዶች

ከአገርዎ ለመውጣት ያስነሳዎት ምክንያት ጋር የተያያዙ ናቸው ብለው ካመኑ ሌሎች ሰነዶችንም ማምጣት ይችላሉ።

እባክዎ ይህን ያስተውሉ፤ ምንም ሰነድ ባይኖርዎትም ከUNHCR ጋር መመዝገብ ይችላሉ።

በ0911633466 ያለውን የምዝገባ ስልክ መስመር መደወል ወይም በWhatsApp 0910019417 / 0916998581 መገናኘት ይችላሉ። ከUNHCR ጋር በትሪፖሊ ወይም በሌላ ቦታ ለመገናኘት ቀጠሮ ይሰጥዎታል።

በ0911633466 ያለውን የምዝገባ ስልክ መስመር መደወል ወይም በWhatsApp 0910019417 / 0916998581 መገናኘት ይችላሉ። ከUNHCR ጋር በትሪፖሊ ወይም በሌላ ቦታ ለመገናኘት ቀጠሮ ይሰጥዎታል።

በ0911633466 ያለውን የምዝገባ ስልክ መስመር መደወል ወይም በWhatsApp 0910019417 / 0916998581 መገናኘት ይችላሉ። ወደ ትሪፖሊ ያለው የUNHCR ቢሮ ወይም ሌላ የምዝገባ እንቅስቃሴ የሚካሄድበት ቦታ ለመሄድ ቀጠሮ ይሰጥዎታል።

ፋይልዎ ተዘግቶ ወይም ተሰናክሎ ከሆነ፣ በ0911633466 ያለውን የምዝገባ ስልክ መስመር መደወል ወይም በWhatsApp 0910019417 / 0916998581 መገናኘት እና ቀጠሮ ማያዝ ይኖርብዎታል። በቀጠሮው ቀን፣ UNHCR ፋይልዎን እንደገና ለመክፈት ወይም ለማንቃት የሚያስፈልጉ መረጃዎችን ለመሰብሰብ ፎርም እንዲሞሉ ይጠይቃል። እባክዎ ፓስፖርትዎን እና ሁሉንም የግል መታወቂያ ሰነዶችዎን ይዘው ይመጡ።

UNHCR በእስር ማዕከላት ውስጥ የመመዝገብ ሂደት አያካሂድም። ነገር ግን UNHCR እንዲፈቱ ይጠይቃል፣ ከተፈቱ በኋላ የመመዝገቢያ ቀጠሮ ይሰጥዎታል።